August 25, 2026
Please enable JavaScript in your browser to complete this form.
Name

የአንጾኪያ ቤተ ክርስቲያን የለውጥ ዝግጁነት መለኪያ

የአንጾኪያ ኢትዮጵያውያን ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን ለለውጥ ዝግጁ ነችን? ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ጥያቄዎች ይህንን ዝግጁነት ለመፈተን የተዘጋጁ ናቸው። መጠይቁ ሃምሳ ጥያቄዎችን የያዘና በነፍስ ወከፍም ሆነ በንኡስ ቡድኖች መሞላት የሚችል ነው ። የዚህ መጠይቅ አላማ በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ ጤናማ የሆነ ውስጣዊና ውጫዊ እድገትን ለማምጣት የሚያዘጋጅ መንደርደሪያ ነው። ጥያቄዎችን ስታነቡ፣ በመጀመሪያ በአእምሮአችሁ የሚመጣውን መልስ በመምረጥ ወደ ሚቀጥለው ጥያቄ እለፉ። እግዚአብሔር ይባርካችሁ።
1) ቤተ ክርስቲያናችን የጠፉትን ለመድረስ ጠንካራ መሻት አላት።
2) ቤተ ክርስቲያናችን በማያስፈልጉ ልምምዶች የተያዘች አይደለችም።
3) በቤተ ክርስቲያናችን ያሉ ብዙ ሰዎች እምነታቸውን በአብዛኛው ጊዜ ለሌሎች ይመሰክራሉ።
4) የቤተ ክርስቲያናችን አባላት በውጭ ካሉት ጋር የዳበረ ግንኙነት አላቸው ።
5) መጋቢዎቻችንና ሌሎች የአመራር አባላት በክርስቶስ ወንጌል ሌሎችን ለመድረስ መሻት አላቸው።
6) የቤተ ክርስቲያናችን አባላት በውጭ ላሉት አይከብዱም (ጥሩ ወዳጅነት አላቸው) ።
7) አባላቶቻችን አንድነት አላቸው፤ ዋና ትምህርት ባልሆኑ ጉዳዮች አይጣሉም ።
8) በጉባዔ አምልኮአችን ውስጥ ያላመነ ሰው ቢመጣ በጣም አይከብደውም
9) ባለፉት አምስት አመታት፣ ቤተ ክርስቲያናችን ለውጥ ውስጥ አልፋለች ፤ ለውጡንም በተገቢ መንገድ አስተናግዳለች።
10) በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ በተለያየ ምክንያት የተሰበሰቡ ሕቡእ (ስውር) ቡድኖች የሉም።
11) ቤተ ክርስቲያናችን በብዙ ሐሴትና ደስታ ትታወቃለች።
12) የቤተ ክርስቲያናችን የአምልኮ መርሃ ግብር ቢለውጥ የሚበሳጩ አባላት አይኖሩም ፣ ቢኖሩም ጥቂት ሰዎች ብቻ ናቸው።
13) አባላቶቻችን በሙዚቃና በቤተ ክርስቲያናችን የአምልኮ አይነት አይጨቃጨቁም።
14) የአምልኮ ጉባዔያችን በአንድነትና በደስታ የተሞላ ነው።
15) በየሳምንቱ በቤተ ክርስቲያናችን የሚመጡ እንግዶች ብዙ ናቸው።
16) በየሳምንቱ ብዙ የቤተ ክርስቲያናችን አባላት እንግዶችን ይጋብዛሉ።
17) ወንጌልን መስበክ በቤተ ክርስቲያናችን ቅድሚያ የሚሰጠው ነገር ነው።
18) ባለፉት አስር አመታት ውስጥ ዋና የሚባል ችግር( ጥል) በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ አጋጥሞ አያውቅም።
19) አዳዲስ አባላት እንዲሁም አዳዲስ ክርስቲያኖች በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ በቶሎ ይታቀፋሉ ያገለግላሉም።
20) በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ ለማያምኑ ሰዎች ሁል ጊዜ ይጸለያል
21) ቤተ ክርስቲያናችን የሚታወቅና ግልጽ የሆነ ራእይ ( Vision Statement) አላት።
22) አባላቶቻችን ለቤተ ክርስቲያን ንብረት ይጠነቀቃሉ።
23) በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ ሃይል ያላቸው ( በተለያየ አይነት መንገድ ተጽእኖ የሚያሳድሩ) ቡድኖች የሉም።
24) የሚፈልጉትን ሁሉ ለማግኘት ሌሎችን የሚጫኑና የሚያስፈራሩ ሰዎች በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ የሉም።
25) የቤተ ክርስቲያናችን አባላት ከሙሉ ጊዜ አገልጋዮች ጋር ጥሩ የሆነ የሥራ ግንኙነት አላቸው።
26) የማያምኑ ሰዎችን በመጋበዝ ቤተ ክርስቲያኔንና ስፍራዋን በማሳየቴ ደስተኛ ነኝ ወይም ኩራት ይሰማኛል።
27) የሕጻናት ማስተማሪያ ክፍሎቻችን ንጹህና ሕጻናት የሚያስፈልጓቸው ነገሮችን ሁሉ ያሟሉ ናቸው።
28) ቤተ ክርስቲያናችን ለሕጻናትንና ራሳችውን መከላከል ለማይችሉ ሁሉ ጥበቃ ያላት ከአደጋ የተጠበቀ ስፍራ ነች።
29) በጣም ጥሩ የሆኑ አነስተኛ ቡድኖችና የሰንበት ትምህርት ቤቶች በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ ይገኛሉ።
30) ቢያንስ ግማሽ የሚሆኑ አባላቶቻችን በአነስተኛ ቡድኖችና በሰንበት ትምህርት ቤቶች የታቀፉ ናቸው።
31) በቤተ ክርስቲያናችን በየጊዜው ጤናማ የሆኑ አነስተኛ ቡድኖችና የሰንበት ትምህርት ክፍሎች ይመሰረታሉ።
32) ስለክርስትና ምንም የማያውቅ ሰው በሰንበት ትምህርታችንና በንዑስ ቡድኖቻችን ውስጥ ቢገባ ባይተዋርነት አይሰማውም።
33) ወንጌልን ውጤታማ በሆነ መንገድ ለማሰራጨት አባላቶቻንን ለለውጥ ዝግጁ ናቸው።
34) የቤተ ክርስቲያን መሪዎቻችን ስለወንጌል ሲባል ምቾቶቻችንን እንድንተው ዘወትር ያበረታቱናል እንዲሁም ይመክሩናል።
35) በቤተ ክርስቲያናችን ክፍፍልን የሚያመጡ ጤናማ ያልሆኑ ስብሰባዎች (ቡድኖች) የሉም።
36) አባላቶቻችንን የጸሎት ሰዎች ናቸው።
37) ስንለወጥ፣ ለለውጡ በመጸለይ እንተጋለን።
38) መጋቢዎቻችንና ሌሎች የቤተ ክርስቲያናችን አመራር አካላት ባለ ራዕዮች ( ሊለካ የሚችል እቅድ ያላቸው) ናቸው።
39) አባላቶቻችን ለውጥን በዝግጁ መንፈስ ይቀበላሉ።
40) ውጤታማ የሆነና አዳዲስ አባላቶች የሚያልፉበት የትምህርት ክፍል አለን።
41) የቤተ ክርስቲያን አመራር ከአባላቶች ብዙ ይጠበቃሉ፤ አባላትም ከራሳቸው ብዙ ይጠብቃሉ።
42) አባላቶቻችችን ሌሎችን በወንጌል ለመድረስ ዋጋ በመክፈል ያገለግላሉ።
43) የቤተ ክርስቲያን መሪዎቻችን ትልቅ የግንኙነት ክህሎት (Relational Skill) ያዳበሩ ናቸው።
44) በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ አይነኬ የተባሉ የማይለወጡ ምንም ነገሮች የሉም።
45) አባላቶቻችን በአገልግሎት ለመሳተፍ ጠንካራ ፍላጎት ያሳያሉ።
46) በቤተ ክርስቲያናችን ግጭት የሚፈታበት ጤናማ የሂደት መንገድ አለ።
47) ባለፉት አምስት አመታት ውስጥ በቤተ ክርስቲያን ባለኝ አካሄድ (አገልግሎት፣ ሃላፊነት፣ ተሳትፎ) ላይ ጥሩ ለውጥ አድርጌያለሁ ( በቤተ ክርስቲያን ከአምስት አመታት በታች ከቆያችሁ፣ እነዚህን አመታት በማሰብ ምላሽ ስጡ)።
48) በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ የሚደሩጉ ዋና አመታዊ የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባዎች (Business meetings) አያስፈሩኝም።
49) በምንኖርበት ማህብረ ሰብ ውስጥ ወሳኝ ሚና ለመጫወት ቤተ ክርስቲያናችን በብዙ መንገድ መለወጥ ይገባታል።
50) በምንኖርበት ማህበረ ሰብ ውስጥ ያ መሪዎችና ሰራተኞች ስለቤተ ክርስቲያናችን በጎ አመለካከት አላቸው።